የማዕድ ማጋራት መርሀ ግብር ተካሄደ ።

የማዕድ ማጋራት መርሀ ግብር ተካሄደ ።

በኮንሶ ዞን በኮልሜ ወረዳ በአባያና ገልገሌ ቀበሌያት የፋስካ በዓልን ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት መርሀ ግብር ተካሄደ ።

#ሚያዚያ 04/2018ዓ/ም :በኮልሜ ወረዳ የአባያና የገልገሌ ቀበሌያት አመራሮችና ህብረተሰብ ድጋፍን አሰባስበው የወረዳው ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ካቢነሽ ካፒኖን ጨምሮ የወረዳው ወጣቶች በጎ ፈቃድ አመራሮች በተገኙበት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙት አቅሜ ደካሞች የአልባሳት ፣የእህልና ለዓመት በዓል የሚሆን ምግብ ነክ ድጋፎችን አድርገዋል ።

“በጎ ተግባራትን በማጠናከር ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉት አካላትን የመደገፍ ሥራን ማጠናከር ያስፈልጋል “ሲሉ የኮልሜ ወረዳ ወጣቶች በጎ አገልግሎት ኃላፊ አቶ አበል አንሲያ አሳስበዋል ።

ችግርተኞችን መደገፍ በበዓል ወቅት ብቻ ሳይሆን ሁልጊዜ :ክትትል በማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍ መስጠት የሁሉም ሰው ግንባር ቀደም ተግባር መሆን አለበትም ብለዋል ።

በወረዳው ደረጃ ከትላንት ጀምሮ በተለያዩ ቀበሌያት ድጋፉ ተጠናክሮ መቀጠሉን የገለፁት አቶ አበል ፤በተመሣሣይ ግለት በወረዳው ሁሉም ቀበሌያት ተግባሩ መቀጠል አለበት” ሲሉ ድጋፎች በተደረጉባቸው ቀበሌያት ተገኝተው መረጃ አድርሰውናል ።

Comments

No comments yet. Why don’t you start the discussion?

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *